አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ለዋናው መስሪያ ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች ከማርሚክ የማማከር ሥራዎች ድርጅት ጋር በመተባበር ስልጠና እየሰጠ ይገኛል::
ስልጠናው በስትራቴጂክ አመራር፣በውጤታማ የቅርንጫፍ ሥራ አመራር፣በደንበኞች ግንኙነት፣በብድር ስጋት ሥራ አመራር እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያታኮረ ነው::
ስልጠናው በማርሚክ የማማከር ሥራዎች ድርጅት መስራች እና ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ዶ/ር እመቤት መለሰ እና ሌሎች ተባባሪ አሰልጣኞች ይሰጣል::
ስልጠናው ከሐምሌ 12-13፣ 2018 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ኢትዮ በርኖስ ሆቴል መሰጠቱን ይቀጥላል::
ስኬትን በተግባር!
አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ
