አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ከታክስ በፊት 47 ሚሊዮን ብር አተረፈ!

“እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!
የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ በ2023/24 ሒሳብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ጥሩ ውጤት ማስመዝገቡን አብስሯል፡፡ በቀረበው ሪፖርት መሠረት ባሳለፍነው የሒሳብ ዓመት ከታክስ በፊት 47 ሚሊዮን ብር አትርፏል፡፡ ለዚህ ውጤት መመዝገብ ከፍተኛውን ድርሻ ላበረከታችሁ የተከበራችሁ ውድ ደንበኞቻችን፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ እና የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም ሠራተኞቻችን ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
በሂሳብ ዓመቱ ብር 232 ሚሊዮን አጠቃላይ ገቢ የተገኘ ሲሆን በዓመቱ ውስጥ የነበረው የወጪ አፈፃመማችን 183 ሚሊዮን ብር ሲሆን 47 ሚሊዮን ብር ትረፍ አትር÷ል፡፡ ለተገኘው ትርፍ ተቋማችን የተገበራቸው የወጪ ቅነሳ ስትራቴጂዎች ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክቷል።
ተቋማችን በስምንት ክልሎች 42 ቅርንጫፍ በመክፈት ከ95,000 በላይ ደንበኞች ያሉት ሲሆን አጠቃላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ብር 1.8 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ የብድር አገልግሎት ለ8250 ደንበኞች አቅርቧል፤ የተሰጡ ብድሮች ለግል ፍጆታ ብድር፣ ለቢዝነስ ማስፋፊያ፣ ለግብርና ብድር፣ ለቤት መስሪያና ማደሻ እና ለተሽከርካሪ ግዥ ብድር ለማኅበረሰባችን ተደራሽ አድጓል፡፡
ተቋማችን በ21 ሚሊዮን ብር ካፒታል ሥራ የጀመረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የተከፈለ ካፒታል ብር 136 ሚሊዮን እንዲሁም ጠቅላላ የተቋሙ ሃብት ብር 1.9 ቢሊዮን ደርሷል፡፡
የተቋማችን የሦስት ዓመት መሪ ዕቅድን መሰረት አድርጎ እየተተገበረ የሚገኘው የሪፎርም ስራ ፍሬያማ በመሆኑ የተበላሹ ብድሮች በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሶ ተቋማችን ደህንነቱ የተጠበቀ የፋይናንስ ተቋም እንዲሆን፤ እንዲሁም የወጪ ቅነሳ እንቅስቃሴያችን ውጤታማ እንዲሆን አስችሏል። ተቋማችን አገልግሎቶቹን ለደንበኞቻችን ምቹ እንዲሆኑ ለማስቻል የኮር ባንኪንግ እና አዳዲስ የድጅታል ባንኪንግ አገልግሎቶችን በመዘርጋት እውን ለማድረግ ተግቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ይህም ለደንበኞቻችን አገልግሎትና ተያያዥ ሥራዎች መቀላጠፍ ጉልህ አስተዋፅኦ በማበርከት ወጪን ለመቀነስ ያስችላል።
በሌላ በኩል ባጠናቀቅነው ሂሳብ ዓመት የተቋማችን ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች የገጠሙት ቢሆንም፣ እነዚህን ተግዳሮቶች በመቋቋም ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገብ መቻላችን የተቋማችንን ጥንካሬ ብሎም አይበገሬነት ማሳያ ነው።
በተገኘው አመርቂ ውጤት በመበረታታት በአዲሱ ሒሳብ ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ በበለጠ ተነሳሽነትና ትጋት መስራት ይጠበቅብናል።የተቋማችን የዳይሬክተሮች ቦርድ እና ሥራ አመራር አባላት የሚሰጡትን አቅጣጫ መሰረት በማድረግ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እና የላቀ አገልግሎት በማቅረብ የደንበኞቻችንን እርካታ ከፍ ለማድረግ በትጋት እየሠራን ሲሆን በመጨረሻም ደንበኞቻችን አብራችሁን በመሆን ለውጤቱ መሳካት ላበረከታችሁት አስተዋፅኦ በድጋሚ እያመሰገንን፣ በ2017 ሂሳብ ዓመትም ተቋማችን ተጨማሪ ቅርንጫፎችን በሁሉም ክልሎች በመክፈት 1.2 ቢሊዮን ብር በላይ አክሲዮኖችን መሸጥ፣ 200,052 ደንበኞችን በማፍራት 3.3 ቢሊዮን ብር የተቀማጭን ገንዘብ በመሰብሰብ ለ20,002 የብድር ደንበኞች 3.6 ቢሊዮን ብር ብድር ለደንበኞች ያቀርባል። እንዲሁም የአክሲዮን ትርፉን በአንድ ሺህ ብር አምስት መቶ ብር ለማከፋፈል በትኩረት እየሠራ ይገኛል፡፡
አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ
ስኬትን በተግባር!

1 thought on “አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ከታክስ በፊት 47 ሚሊዮን ብር አተረፈ!”

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top