እንኳን ለ 2016 ዓ.ም በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ!

ለአኩፋዳ ማይክሮፋይናንስ ነባር ባለአክሲዮኖች የቀረበ የተጨማሪ የአክሲዮን ግዢ ጥሪ!

ታህሳስ 23/2015 ዓ/ም በተካሄደው የአኩፋዳ ማይክሮፋይናንስ ተቋም 1ኛ መደበኛ እና 1ኛ አስቸኳይ የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ የማይክሮፋይናንሳችን ካፒታል ወደ አምስት ቢሊየን ብር እንዲያድግ በተወሰነው መሰረት እያንዳንዳቸው ብር 1000 ዋጋ ያላቸው ቁጥራቸው 4,966,232 የሆኑ አዲስ አክሲዮኖችን ተቋማችን ለሽያጭ አቅርቧል፡፡

በመሆኑም በሀገሪቱ የንግድ ሕግ ነባር ባለአክሲዮኖች ባላቸው የቅድሚያ መብት መሰረት አዲስ የወጡ አክሲዮኖችን በማይክሮፋይናንሱ ውስጥ ባላችሁ የአክሲዮን መጠን የተደለደለላችሁ ሲሆን መግዛት የምትፈልጉትን አክሲዮኖች ጠቅላላ ዋጋ 25 % ቅድሚያ በመክፈል እስከ መስከረም 15/2016 ዓ/ም ድረስ በማይክሮ ፋይናንሱ የአክሲዮን ሽያጭ እና አስተዳደር ክፍል በመቅረብ እንዲሁም በሁሉም የተቋሙ ቅርንጫፎች በመሄድ እንድትገዙ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪ እያቀረበ ተጨማሪ መረጃዎችን በተቋማችን ድህረ ገፅ https://akufadamf.com ላይ በመግባት የተሟላ መረጃ የምታገኙ መሆኑን እየገለፅን የዚህ ታላቅ ዕድል ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።

የዳይሬክተሮች ቦርድ
ለበለጠ መረጃ
አኩፋዳ ማይክሮፋይናንስ ተቋም አ.ማ
ዋና መስሪያቤት
ጠባሴ ጻድቃኔ ሕንጻ 6ኛ ፎቅ
አክሲዮን ሽያጭና አስተዳደር ክፍል
ስ.ቁ፡- 0988999996/97/98/

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top