News

News

የባለአክሲዮኖች 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 2ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ማስታወቂያ

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ አድራሻ፡-በአማራ ብሔራ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ደብረ ብርሃን ከተማ፣ ቀበሌ 02፣ የዋና ንግድ ምዝገባ ቁጥር AM/BD/3/0004970/2014፣ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ሥራ ፈቃድ ቁጥር MF/055/2022፣ የተፈረመ ካፒተል ብር 33,768,000.00 (ሰላስ ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስልሳ ስምንት ሺ ብር) ሲሆን የባለአክሲዮኖች 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 2ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ህዳር 29 ቀን 2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡ 00 ሠዓት ጀምሮ በአማራ ክልላዊ መንግስት ደብረ ብርሃን ከተማ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ አዳራሽ ውስጥ ስለሚካሄድ ባለአክሲዮኖች በአካል ወይንም በወኪሎቻችሁ አማካኝነት በተጠቀሰው ጊዜና ቦታ በስብሰባው ላይ እንድትገኙ የዳይሬክተሮች ቦርድ በአክብሮት ጥሪውን ያቀርባል፡፡ የሁለተኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ አጀንዳዎች የሁለተኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች ማሳሰቢያ፦ 1. በጉባኤው ላይ በአካል የምትገኙ ባለአክሲዮኖችም ሆኑ ወኪሎች የታደሰ መታወቂያ፣ ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ ይዛችሁ እንድትቀርቡ እናሳስባለን፡፡ 2. በጉባኤው ላይ በአካል መገኘት የማይችሉ ባለአክሲዮኖች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ አስከ ህዳር 29 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ ብቻ ደብረ ብርሃን ከተማ ፃድቃኔ ሕንፃ 6ኛ ፎቅ ከሚገኘው የተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በመቅረብ የውክልና ቅፅ በመሙላት ወይም አግባብ ባለው የመንግስት አካል የተረጋገጠ በስብሰባ ላይ ለመሳተፍና ድምፅ ለመስጠት የሚያስችል የውክልና ስልጣን ማስረጃ ዋናውንና ፎቶ ኮፒ ይዘው በመቅረብ ወይም የሞግዚትነት ማስረጃ በማቅረብ በጉባኤው ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡ አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማህበር የዳይሬክተሮች ቦርድ

የባለአክሲዮኖች 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 2ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ማስታወቂያ Read More »

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማኅበር 2ኛ መደበኛ እና 2ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባለት የምርጫ ውጤትን ስለማሳወቅ

ዳር 29 /2016 ዓ.ም ደብረብርሃን አጼ ዘርዓ ያዕቆብ አዳራሽ በተከናወነው የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ. ባለአክሲዮኖች 2ኛ መደበኛ እና 2ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከነበሩት አጀንዳዎች መካከል አንዱ ማይክሮ ፋይናንሱን ለሚቀጥሉት 3 ዓመታት የሚመሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ማከናወን እንደ ነበር ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት በእለቱ በተከናወነው የምርጫ ስነ ስርአት አስራ ዘጠኝ ሰዎች የተጠቆሙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል በትምህርት ዝግጅት ፣ በስራ ልምድ ፣ በብሄራዊ የባንክ መመሪያ ለእጩ ዳይሬክተርነት የተቀመጡ መስፈርቶችን ያሟሉ እንዲሁም በዳይሬክተርነት ለማገልገል ፈቃደኛ ሆነው ራሳቸውን ለጉባኤተኛው ካስተዋወቁና በመጨረሻ እጩነት ከቀረቡት 19 ተወዳሪዎች መካከል ከዚህ በታች የተዘረዘሩት 9ኝ እጩዎች ባገኙት የባለአክሲዮን ድምጽ መሰረት እጩ ዳይሬክተር ሆነው የተመረጡ ሲሆን 3ቱ ተጠባባቂ እጩ ዳይሬክተሮችም ተመርጠዋል፡፡ የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ ምርጫ በኢትዮጽያ ብሔራዊ ባንክ ጸድቀው የስራ ርክብክብ እስከሚደረግ ድረስ ውጤቱን ለባለ አክሲዮኖች በሙሉ ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ በዚህ መሰረት እንዲቀመጥ አድርጓል፡፡ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ዕጩ ያገኙት ድምፅ   ተመራጭ ያገኙት ድምጽ 1 ሮቤል ንጉሴ  ኃይሉ 109759 2 ዲ/ን ካሳሁን ደገፉ ገ/ሃና 106875 3 አቶ ተፈራ ወ/አገኝ ገድሌ 87651 4 አቶ እምሻው ተፈራ ተክሌ 83859 5 አቶ ከለላው ጎሽሜ ክፍሌ 83502 6 አቶ ጊዜው ሽመልስ ኃ/ማርያም 83123 7 አቶ በሱፈቃድ ተስፋዬ አለማየሁ 82728 8 አቶ ተመስገን ወርቁ ላቀው 79830 9 ሊ/ካ በሃይሉ በቀለ 76680 10 አንበስ ግርማ ወ/መድህን 67992 11 አቶ በየነ አየለ ታምሩ 66573 12 ዲ/ን ወ/ጻዲቅ ቃኘው 65522 13 አለባቸው ጎሽም አዘረፍ 64750 14 አቶ ስንታየሁ አንባቸው 55423 15 መ/ቀ/ገ/ ሀይሌ አየለ 54670 16 አቶ ደበበ ደጀኔ ተሰማ 53123 17 ቀ/ዶ/ ሀይሉ ተረፈ 53041 18 አቶ ጋሻው ጎረምስ ማገር 43012 19 ዲ/ን ወ/ኢየሱስ አየለ አግዝ 41443 የድምፅ ቆጣሪ ስም                                                    ወ/ሮ አሰለፈች ጎሽሜ ክፍሌ ተወካይ አቶ ኃይሉ ጥላሁን ገሰሰ   

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አክሲዮን ማኅበር 2ኛ መደበኛ እና 2ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባለት የምርጫ ውጤትን ስለማሳወቅ Read More »

Scroll to Top