News

News

<<የወረዳችንን ወጣቶችና አርሶ አደሮች በፋይናንስ ተደራሽ ማድረግ በክልል ደረጃ የጀመርነው የ25 ዓመታት ተሻጋሪ የልማት ዕቅድ አስኳል ነው>>     ~~ አቶ አከበረኝ አላማው፣ የእንሳሮ ወረዳ አስተዳዳሪ አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ እና እንሳሮ ወረዳ በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረሙ      እንሳሮ፣ ለሚ ||

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ በስትራቴጂ ያስቀመጠውን የፋይናንስ ተደራሽነት እና አካታችነት (Financial Inclusion and Access to Finance for the hard-to-reach communities) ላይ በጋራ ማኅበረሰቡን ለማገልገል ያለመ የትብብር ማዕቀፍ ዛሬ መስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም በእንሳሮ ወረዳ ለሚ ከተማ ስምምነቱ ተፈርሟል። ስምምነቱን የእንሳሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አከበረኝ አላማው እና የአኩፋዳ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብርሃም ወዳጆ ተፈራርመዋል። ይህ አጋርነት በዋናነት የወረዳውን ወጣቶችና ሴቶች የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች፣ የአርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት እና የቴክኖሎጂ ግዢ፣ የመንግሥት ሠራተኞች እና የመኖሪያ ቤት ማኅበራት ብድር ለማቅረብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳለው የአኩፋዳ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አብርሃም ገልፀዋል። <<የወረዳችንን ወጣቶችና አርሶ አደሮችን በፋይናንስ ተደራሽ በማድረግ በክልል ደረጃ የጀመርነውን የ25 ዓመታት ተሻጋሪ የልማት ዕቅድ ለማሳካት ዓይነተኛ ሚና አለው፣ አኩፋዳም በተግባር ሕዝባችን ውስጥ ሆኖ እያገለገለን ነው፣>> ያሉት ክቡር አቶ አከበረኝ፣ በጋራ ለጋራ ኤኮኖሚያዊ ዕድገት (shared economy) እንዲረጋገጥ እንሠራለን በለዋል። የኦፕሬሽን ዋና መኮንን አቶ ከፋለ ጣሠው በበኩላቸው ከአገልግሎት ጥራት እና ተደራሽነት አንፃር በቴክኖሎጂ ታግዞ ሕዝቡን ማገልገል ቀዳሚ የአኩፋዳ ፍልስፍና መሆኑን፣ የኦፕሬሽን ልኅቀት (Operational Excellence) ለማምጣት እየተሠራ መሆኑን ለወረዳው መስተዳድር አረጋግጠዋል። አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ስኬትን በተግባር !

<<የወረዳችንን ወጣቶችና አርሶ አደሮች በፋይናንስ ተደራሽ ማድረግ በክልል ደረጃ የጀመርነው የ25 ዓመታት ተሻጋሪ የልማት ዕቅድ አስኳል ነው>>     ~~ አቶ አከበረኝ አላማው፣ የእንሳሮ ወረዳ አስተዳዳሪ አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ እና እንሳሮ ወረዳ በጋራ ለመሥራት የመግባቢያ ሥምምነት ተፈራረሙ      እንሳሮ፣ ለሚ || Read More »

ምክክር ተደረገ🌼🌼

የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ዋናው መሥሪያ ቤት የሥራ መሪዎች በሸዋሮቢት ከተማ ተገኝተው ከሸዋሮቢት ቅርንጫፍ ባልደረቦች፣ ከቀወት እና ሸዋሮቢት ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ እና የአጥቢያ አስተዳዳሪዎች ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ምክክር ተደርጓል። ስኬትን በተግባር!

ምክክር ተደረገ🌼🌼 Read More »

የቤት ማኅበራት ውይይትና የአኩፋዳ ዝግጁነት❗️❗️

በተለምዶ 100 ማኅበራት እየተባሉ  ከሚጠሩት  አባላት ጋር የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ውይይት አካሄደ የደብረ ብርሃን ከተማ ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ነቢዩ ባዩ ተቋማቸው እና መሬት መምሪያ  ለ100 የቤት ማኅበራት በቦታ ዝግጅት እና የካሳ ክፍያ አስመልክቶ የተሄደበትን ርቀት ለውይይት መነሻ  ሰነድ  አቅርበዋል። የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ የተከበሩ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው ከተማው ከ2008 ዓ.ም አንስቶ እስከ 2015/16 ዓ.ም ድረስ በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ዜጎች ቦታ አመቻችቶ የቤት ተጠቃሚ  ማድረጉን አስረድተዋል። በመድረኩም ሰፊ ውይይት ተደርጎ የመሬት ካሳ ግምቱን  እስከ መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሁሉም የማኅበራት አባላት አስገብተው እንዲያጠናቅቁ  አቅጣጫ  ተቀምጦ መግባባት ላይ ተደርሷል። የውይይት ተሳታፊዎችም እስከ መስከረም 15/2018 ዓ.ም ድረስ አስገብተው ለማጠናቀቅ መስማማታቸውን በሰጡት አስተያየት አረጋግጠዋል። በስብሰባው የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ዋናው መሥሪያ ቤት የኦፕሬሽን እና ሪሶርስ ሞቢላይዜሽን ዲቪዥን ሥራ አስኪያጅ አቶ ሥዩም ተፈራ ተገኝተው ማብራሪያ ሰጥተዋል። አኩፋዳ ወጣቶች የቤት ባለቤት እንዲሆኑና የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ ለ100 ማህበራት አባላቶች በተመጣጣኝ ወለድ ብድር ማቅረብ እና ለአባላቱ ቁጠባ ጠቀም ያለ ወለድ እንደሚከፍል ለታዳሚው አብራርተዋል። አገልግሎቱንም ከመስከረም  5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በደብረብርሃን ከተማ በሚገኙት 3ቱም ቅርንጫፎች መገልገል እንደሚችሉ ተገልጿል። ከብድርና ቁጠባ ጋር የተገናኘ የማኅበር አባላት ለሚኖራቸው ጥያቄ ሁሉ:-   +251116377756  +251116377175 ይደውሉ። ስኬትን በተግባር!

የቤት ማኅበራት ውይይትና የአኩፋዳ ዝግጁነት❗️❗️ Read More »

ልዩ ጥቆማ!

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ከደብረብርሃን ፋና ኤፍ.ኤም 94.0 ጣቢያ ጋር በመተባበር በየሳምንቱ ዘወትር እሁድ ከቀኑ ከ7፡30-7፡50 ድረስ ልዩ ልዩ መረጃዎችን ወደ ክቡራን አድማጭ ደንበኞቹ ለማድረስ ዝግጅቱን አጠናቋል። የመጀመሪያው መሠናዶ ነገ እሁድ መስከረም 4 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናበስራለን። አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማስኬትን በተግባር!

ልዩ ጥቆማ! Read More »

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ እና የሰሜን ሸዋ ዞን ትምሕርት መምሪያ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ

በዞኑ ውስጥ የሚገኙ ትምሕርት ቤቶችን፣ መምሕራንን እና ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጋራ መግባቢያ ሰነድ ዛሬ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በደብረብርሃን ከተማ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በዋናነት በአገር ልማት እና ማኅበረሰብ ዕድገት ላይ እየሰሩ በሚገኙት በሁለቱ ተቋማት መካከል የዳበረ ሐብት አስተዳደር እና የፋይናንስ አቅርቦት ላይ በትብብር ለመስራት ያለመ ነው። በዚህ የመግባቢያ ስምምነት መሠረት በጥቅል ልማትና ማኅበረሰብ ዕድገት፣ በተቋሞቻቸው ሀብት አስተዳደርና ትብብር፣ በተመጋጋቢ ፕሮሞሽን፣ ገጽታና አቅም ግንባታ ዘርፍ በጋራ ለመስራት በማሰብ ነው። የዞኑ ትምሕርት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ብርሃኑ የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብርሃም ወዳጆ ተቋሞቻቸውን ወክለው ስምምነቱን የፈረሙ ሲሆን፣ ከጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮም ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል። በዞኑ ከ1,119 በላይ ትምሕርት ቤቶች ያሉ መሆኑን የጠቀሱት ም/መምሪያ ኃላፊው፣ በእነዚህ የትምሕርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ መምሕራን እና ተማሪዎችን ጨምሮ ትምሕርት ቤቶች የፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስትራቴጂያዊ ስምምነት እንደሆነ ጠቅሰዋል። የአኩፋዳ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብርሃም በበኩላቸው የዞኑን የትምሕርት ሥርዓት መደገፍ እና የፋይናንስ አገልግሎት ማቅረብ የተቋሙ ተልዕኮ በመሆኑ አጠናክረን በአገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበር መሆኑን አብራርተዋል። አኩፋዳ በ7 ክልልሎችና ከተማ አስተዳደሮች 45 የነበሩትን ቅርንጫፎች ወደ 55 እያሳደገ ሲሆን ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት ስትራቴጂ ተነድፎ እየተሰራ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል። አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማስኬትን በተግባር!

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ እና የሰሜን ሸዋ ዞን ትምሕርት መምሪያ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ Read More »

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ለሐበሻ አረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ልማት ድርጅት የምግብ እሕል ድጋፍ አደረገ

በደብረብርሃን ከተማ የሚገኘው የአረጋውያን መርጃ ድርጅት በርካታ ጧሪ የሌላቸውን አረጋውያን እና ምስኪኖችን ከወደቁበት እያሰባሰበ የሚንከባከብ አገር-በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው። ሆኖም በሥሩ ከያዛቸው በርካታ ድጋፍ የሚሹ አካላት ቁጥርና የችግሩ ውስብስብነት አንጻር ሰፊ ድጋፍና ዘላቂ የመፍትሔ መንገዶችን ይሻል። ከእነዚህ ፍላጎቶች አንጻር አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ 10 ኩንታል የምግብ እህል በዛሬው ዕለት ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በመርጃ ማዕከሉ በመገኘት ድጋፉን ሰጥቷል።ድጋፉንም የአኩፋዳ የዳይሬክተሮች ቦርድ ም/ሰብሳቢ ዲ/ን ካሣሁን ደገፉ ከተቋሙ የማኔጅመንት አባላት ጋር በጋራ በመሆን በሥፍራው ተገኝተው አስረክበዋል። አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ስኬትን በተግባር!

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ለሐበሻ አረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ልማት ድርጅት የምግብ እሕል ድጋፍ አደረገ Read More »

እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!

ክቡራን የአኩፋዳ ደንበኞች፣ ባለአክሲዮኖች፣ ትጉኃን ሠራተኞቻችን እና መላው ኢትዮጵያውያን እና በመላው ዓለም የምትገኙ አጋሮቻችን እንኳን ለ2018 ዓ.ም በፍቅርና በመተሳሰብ አደረሳችሁ። ይህን አዲስ ዘመን ስንቀበል ተቋማችን በአጭር ጊዜ በከፍተኛ የዕድገትና የውጤታማነት ምዕራፍ ላይ መሆኑ እጅግ አበረታች ነው። በስትራቴጂ ያስቀመጥናቸውን መላውን የአገራችንን ማኅበረሰብ በተለይም የፋይናንስ ተደራሽነት ጉድለት ያለባቸውን አርሶ አደሮች፣ የገጠር ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች፣ የከተማ ወጣቶች እና አነስተኛ ኢንቨስትመንቶችን በበቂ ሁኔታ ፋይናንስ ለማድረግ እየሠራን እንገኛለን። ለዚህ ትልቅ የዕድገት ርዕይ ደንበኞቻችን እና አጋሮቻችን ከጎናችን እንደሚሆኑ በመተማመን አዲሱን ዘመን ጀምረናል። ዘመኑ የፍሬ እና የውጤት እንዲሆን እየተመኘሁ መልካም በዓል እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ። መልካም በዓል🌼🌼🌼 አቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ ገድሌየዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ

እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! Read More »

የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ እና ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን አ.ማ የደብረብርሃን ፋና ኤፍ.ኤም 94.0 በአጋርነት የሚያዘጋጁት የሬድዮ ፕሮግራም ለማዘጋጀትና ለማሰራጨት የሥራ ውል ሥምምነት አደረጉ። አኩፋዳ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ያገኘ የፋይናንስ አገልግሎት ለማኅበረሰቡ የሚያቀርብ ሲሆን ከደብረብርሃን ፋና ኤፍ.ኤም 94.0 ጋር በመተባበር የሬዲዮ ፕሮግራም በማሠራጨት በፋይናንስ አቅርቦት፣ ተደራሽነት፣ በንግድ ሥራና አስተዳደር እና በሥራ ፈጠራና የፋይናንስ ምንጭ ማፈላለግ ዙሪያ በስፋት ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ ፕሮግራም እንዲሆን በጋራ ለመሥራት ከስምምነት ላይ ደርሰዋል። የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብርሃም ወዳጆ በፊርማ ሥነ-ስርዓቱ ወቅት፣ አኩፋዳ ከ156 ሺህ በላይ ደንበኞች ያሉት አዳጊ የሕዝብ ተቋም በመሆኑ አገልግሎቱን በስፋት ለሕዝብ ተደራሽ ለማድረግ ሚዲያን እንደ አንድ የቢዝነስ አጋር እንደሚጠቀም ገልጸዋል። ደብረብርሃን ፋና ኤፍ.ኤም 94.0 በበኩሉ የማህበረሰብን የኤኮኖሚ ዕድገት ከሚወስኑ የፋይናንስ ተቋማት ጋር አብሮ በመስራት በወጣቶች ሥራ ፈጠራና የፋይናንስ አቅርቦት፣ ህብረተሰብን በፋይናንስ-ነክ መረጃዎች ዐቅሙን በመገንባትና ግንዛቤ በመፍጠር የተጣለበትን ግዴታ መወጣት የሚያስችለው መሆኑን የደብረብርሃን ፋና ኤፍ.ኤም 94.0 ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘላለም ገበየሁ አሳውቀዋል። ስኬትን በተግባርአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ

የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ Read More »

የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብርሃም ወዳጆ በግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተዘጋጀው የፋይናንስ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ተሳተፉ።

በግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተዘጋጀው ‘ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ’ በመላ አገሪቱ የፋይናንስ አቅርቦትን ለማጎልበት እና አነስተኛ አርሶ አደሮችን ብድር እንዲያገኙ ለመደገፍ ቁልፍ መሣሪያ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው  አኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ ለግብርናው ዘርፍ ከ120 ሚሊየን ብር በላይ የብድር አቅርቦት በአጭር ጊዜ ማቅረቡን ገልፀው ለአርሶ አደራችን ለውጥና እድገት ብሎም  ለአጠቃላይ  ኢኮኖሚያዊ  ዕድገት  ተቋማችን  የላቀ አስተዋፅኦ እንደሚያደርግ ጨምረው ገልፀዋል።                               

የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብርሃም ወዳጆ በግብርና ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተዘጋጀው የፋይናንስ የማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ ተሳተፉ። Read More »

“የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫችን ነው”

የአኩፋዳ ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ከተቋሙ የሥራ አመራር አባላት እና ከቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች ጋር የ2024/25 ሒሳብ ዓመት የአፈጻጸምን አስመልክቶ የምክክር መድረክ አካሄደ። በመድረኩ የተገኙት አቶ ተፈራ ወንድማገኘሁ፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ም/ሰብሳቢ ዲ/ን ካሣሁን ደገፉ ከ45ቱ ቅርንጫፎች ጋር በጋራ የዓመቱን አፈጻጸም ግምገማ በማድረግ በተያዘው የ2025/26 ተቋማዊ ውጤታማነትን እና ትርፋማነትን በማረጋገጥ ለባለአክሲዮኖች እና ማኅበረሰብ እድገት መሥራት ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን አቅጣጫ ሰጥተዋል። የቦርዱ ሰብሳቢ አክለውም አኩፋዳ በተቋቋመ በአጭር ጊዜ በ7 ክልሎች ከ150 ሺህ በላይ ደንበኞቹን ማገልገል መጀመሩ ትልቅ ስኬት ሲሆን፣ በሂደት ተደራሽነቱን፣ የደንበኞች አያያዝ ሥርዓቱን እና ቅልጥፍናውን በማላቅ ተመራጭ የፋይናንስ ተቋም ለመሆን የጀመረው ጉዞ አመርቂ ነው ብለዋል። ተቋሙ የፋይናንስ አሰራሩን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግ ቴክኖሎጅን ከጅምሩ ለመተግበር አስደሳች ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብርሃም ወዳጆ፣ “የአገልግሎት ቅልጥፍናችን እንዲሻሻልና የደንበኞቻችንን እርካታ ለማሳደግ የቴክኖሎጅ (ኮር ባንኪንግ፣ የሞባይል ባንኪንግ፣ ወዘተ) በተሟላ ደረጃ ለመተግበር የሚያስችሉ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ማይክሮ ፋይናንስ ተቋሙ 45 ቅርንጫፎችን በመክፈት የፋይናንስ አቅርቦት እያደረገ ይገኛል ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፣ በአጭር ጊዜ 450 ሠራተኞችን በመቅጠር ማኅበራዊና ኤኮኖሚያዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል። በማጠቃለያውም በተጠናቀቀው ሒሳብ ዓመት የተሻለ የኦፕሬሽን አፈጻጸም ላስመዘገቡ ቅርንጫፎች ዕውቅና እና ምስጋና ተበርክቶላቸዋል

“የፋይናንስ አገልግሎት ተደራሽነት ቁልፍ የትኩረት አቅጣጫችን ነው” Read More »

Scroll to Top